የቃል ግጥሞች ማኅበራዊ ፋይዳ - በደቡብ ወሎ ቦረና ወረዳ አርሶ አደሮች ማንጸሪያነት
The Social Benefits of Oral Poetry: Reflections of Farmers’ Life in South Wollo, Borena District
Keywords:
oral poetry, social benefit, good values, bad character, ቃላዊ ግጥም፣ ማኅበራዊ ፋይዳ፣ መልካም ዕሴቶች፣ መጥፎ ባሕርያትAbstract
የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በደቡብ ወሎ ቦረና ወረዳ በሚገኘው አርሶ አደር ማኀበረሰብ ከሚከወኑት ቃል ግጥሞች ማኅበራዊ ፋይዳ ባላቸው ላይ የይዘት ትንተና ማካኼድ ነው፡፡ ጥናቱ ዓይነታዊ የምርምር ዘዴን የተከተለ ሲኾን፣ ቃል ግጥሞችን ከመስክ ለመሰብሰብ ተግባር ላይ የዋሉት የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች ደግሞ ቃለ መጠይቆችና ሰነዶች ናቸው፡፡ በእነዚህ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች የተሰበሰቡት ቃል ግጥሞች በገላጭ የምርምር ዓይነት ይዘታቸው ተተንትኗል፡፡ በትንተናው ወቅት ተግባራዊ ንድፈ ሐሳብ (Functional Theory) ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ከይዘት ትንተናውም ቃል ግጥሞቹ የማኀበረሰቡን መልካም ዕሴቶች የማስተማር ፋይዳ ያላቸው መኾኑን ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ በዚህም ግብረ ገብነትን በሚያንጸባርቁ ቃል ግጥሞች አማካይነት ልጆችን እና ወጣቶችን በማስተማር ገና ከለጋነታቸው ጊዜ ጀምሮ ባሕርያቸውን መቅረጽ እንደሚገባ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቃል ግጥሞቹ በሥራ የመትጋትን ጥቅም ለማኅበረሰቡ የማሳወቅ ፋይዳ እንዳላቸው ተስተውሏል፡፡ ይህ ዓይነቱ ፋይዳ በኅብረተሰቡ ዘንድ የሥራ ፍቅር እንዲኖር ስለሚያደርግ ለኢኮኖሚውና ለማኅበራዊው ልማት የሚያበረክተው አስተዋፅኦ እጅግ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠው ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ቃል ግጥሞቹ መጥፎ ባሕርያትን የመግታት ፋይዳ እንዳላቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህ መሠረት በስንፍና፣ በዳተኝነት፣ በሐሜት፣ በክሕደት፣ በአመንዝራነት፣ ጠንቋይን በማመን፣ በመታበይ (በመኩራት)፣ በሙስና፣ በመሳሰሉት መጥፎ ተግባራት ላይ የተዘፈቁ ሰዎች አድራጎታቸውን ለመቆጣጠርና ለመግታት ሲባል በቃል ግጥሞች አማካይነት በማኅበረሰቡ ሲወገዙ ተስተውሏል፡፡ በመጨረሻም የሥነ ማኅበረሰብ፣ የሥነ ሰብና የታሪክ ምሁራን ማኅበራዊ ፋይዳን በተመለከተ የተነገሩ ሌሎች ቃል ግጥሞችን ከመስክ ሰብስበው ጥናት ቢያደርጉ የወረዳውን ማኅበረሰብ ታሪክ፣ ማኅበራዊ ሕይወት፣ ባህልና ሥነ ልቡና፣ ወዘተ. የበለጠ ለመገንዘብ ያስችላል የሚል ይሁንታ በአጥኚው ቀርቧል፡፡
The primary objective of this study is to conduct a content analysis of the social benefits of oral poems performed within the farming community of the Borena District in South Wollo. The study employed a qualitative research methodology, utilizing interviews and document analysis as data collection methods to gather oral poems from the field. The collected poems were subsequently analyzed using descriptive research, guided by functional theory. The content analysis revealed that oral poems serve several key social functions. Primarily, they are instrumental in teaching and reinforcing the community's positive values. The findings suggest that by transmitting moral lessons to children and youth, oral poems play a crucial role in shaping character from an early age. Furthermore, the analysis indicates that oral poems promote a strong work ethic by informing the community of the importance of hard work. This benefit fosters a collective appreciation for labor, which is highly valued for its contribution to both economic and social development. Conversely, it was found that oral poems also function to curb negative social behaviors. The study observed that individuals engaged in detrimental acts—such as laziness, dishonesty, gossip, betrayal, adultery, belief in witchcraft, arrogance, and corruption—are often subject to social condemnation through these poems, which serve to control and restrain such conduct. Finally, the researcher suggests that further collection and study of oral poems concerning social benefits by sociologists, anthropologists, and historians would provide deeper insights into the history, social life, culture, and mentality of the district's community.
