ZENA-LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures) https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC <p>The Zena-Lissan Journal was started in 1996 by the then Ethiopian Languages Research Centre (ELRC), now the Academy of Ethiopian Languages and Cultures (hereafter AELC), focused especially on the cultures (folklores) and languages of different societies within Ethiopia. Since then, the journal has continued to be published biannually in Amharic and English languages aimed to encourage research and promote dialogue among scholars of interdisciplinary fields.</p> en-US Tue, 27 May 2025 10:57:39 +0000 OJS 3.2.1.3 http://blogs.law.harvard.edu/tech/rss 60 በአማርኛ መማሪያ መፃህፍት ውስጥ የቀረቡ የሰዋሰው ይዘቶች ሰዋሰዋዊነት https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/11359 ጌታሁን አማረ Copyright (c) 2025 https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/11359 Tue, 27 May 2025 00:00:00 +0000 “የአጥር ወፍ አትስማሽ” ሥርዓተ ክዋኔና ፋይዳ በጃቢ ጠህናን ወረዳ '' https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/11595 <p>&nbsp;</p> <p>ይህ ጥናት የአጥር ወፍ አትስማሽ ሥርዓተ ክዋኔና ፋይዳ በጃቢ ጠህናን ወረዳ በሚል ርዕስ<br>የቀረበ ሲሆን ፤ዋና ዓላማው &amp;quot;የአጥር ወፍ አትስማሽ; ሥርዓተ ክዋኔ ማን፣ ምን፣ እንዴት፣<br>መቼ፣ የት፣ እንደሚከበር እና ያለው ፋይዳ ምን እንደሆነ ማሳየት ነው፡፡ ጥናቱ አይነታዊ የምርምር<br>ዘዴን የተከተለ ሲሆን ፤መረጃዎቹ ከካልዓይና ከቀዳማይ የመረጃ ምንጮች ከዐውዳቸው<br>ተሰብስበው “የአጥር ወፍ አትስማሽ” ስርዓተ ክዋኔና ፋይዳን ከሥርዓተ ክዋኔው ጋር በተያያዘ<br>የሚከወኑ ሀገረሰባዊ እምነቶች እና ብሂላዊ ንግግሮችን ምንነት መርምሯል፡፡ የጥናቱ የንሞና ዘዴ<br>ዓላማ ተኮር ሲሆን፤ ከቁልፍና ከተባባሪ መረጃ ሰጪዎች የተሰበሰቡ መረጃዎች ተግባራዊ ፣<br>ተምሳሌታዊ እና ሥነ ልቡናዊ ንድፈ ሀሳቦችን በመጠቀም ተተንትነዋል፡፡ በጥናቱ ውጤት መሰረት<br>የአጥር ወፍ አትስማሽ ሥርዓተ ክዋኔ ሰፊ ጽንሰ ሀሳብን የሚይዝ ሲሆን፤ ከእርግዝና ጀምሮ እስከ<br>ክርስትና ያለውን ጊዜ ሂደት የሚያጠቃልል ነው፡፡ አንዲት ነፍሰጡር እናት መውለጃዋ ሲቃረብ<br>፤ዘመድ ጎረቤቶቿ ምጧ ሳይጠናባት &amp;quot;ከአጥሯ ስር ያለችው ወፍ&amp;quot; እንኳ ሳትሰማ በሰላም<br>እንድትገላገል መልካም ምኞታቸውን የሚገልጹበት ሲሆን፤ ሥርዓተ ክዋኔውን አስመልክቶ ወላዷ<br>በወሊድ ጊዜ የምትመገባቸውን ምግቦች እና ፈሳሾች በጋራ በመሰባሰብ ከማዘጋጀት ጀምሮ እስከ<br>ክርስትና ማስነሳት ድረስ ሊዘልቅ የሚችል ክዋኔያዊ ሥርዓትን የሚያካትት ነው፡፡ ሰዎች<br>ነፍሰጡሯን “የአጥር ወፍ አትስማሽ” በማለት መልካም ምኞታቸውን እንደሚገልጹላት ከመረጃ<br>ሰጪዎች ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ክዋኔያዊ ሥርዓቱ ለነፍሰጡር እናቶች ካላው ኢኮኖሚያዊ፣<br>ማኀበራዊና ሥነ ልቦናዊ ፋይዳ አንጻር ባህላዊ እሴቱን ለወጣቱ ትውልድ የማሳወቅ ሥራ በባህል<br>ቱሪዝም ባለሙያዎች አማካኝነት መሰራት እንደሚገባ ምክረ ሐሳብ በመስጠት ጥናቱ<br>ተጠናቋል፡፡<br>ቁልፍ ቃላት፡- [የአጠር ወፍ አትስማሽ፣ስርዓተ ክዋኔ፣ጃቢ ጠህናን]</p> Mesfin Fekadie Copyright (c) 2025 https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/11595 Tue, 27 May 2025 00:00:00 +0000