ZENA-LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures)
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC
<p>The Zena-Lissan Journal was started in 1996 by the then Ethiopian Languages Research Centre (ELRC), now the Academy of Ethiopian Languages and Cultures (hereafter AELC), focused especially on the cultures (folklores) and languages of different societies within Ethiopia. Since then, the journal has continued to be published biannually in Amharic and English languages aimed to encourage research and promote dialogue among scholars of interdisciplinary fields.</p>Center for Ethiopian Languages and Culturesen-USZENA-LISSAN (Journal of Academy of Ethiopian Languages and Cultures)2222-6028የግብረ ገብ ሐሳቦች በበዓሉ ግርማ ‹‹የህሊና ደወል››
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/13987
<p>ይህ ጥናት ከበዓሉ ግርማ ልቦለዳዊ ሥራዎች አንዱ የሆነውን ‹‹የህሊና ደወል›› እንደገና ያነባል፤ እንደገና<br>ይፈክራል። የአጥኝው የንባብ ቅኝትም የግብረ ገብ ፍልስፍና ጽንሰ ሐሳቦችን ያማከለ ነው። በተደረገው<br>ቅድመ ጥናት የንባብ ጥረት የህሊና ደወልን ከግብረ ገብ ፍልስፍና አንጻር የተነተነ አጥኝ አለመገኘቱ የዚህ<br>ጥናት አነሳሽ ሰበብ ሆኗል። በመሆኑም ጥናቱ ከዚህ በፊት በሌሎች አጥኝዎች ያልታዬ እይታን ስለመያዙ<br>አጥኝው ያምናል። ይህ ጥናት ዓይነታዊ የጥናት ዘዴን የተከተለ በባህል ጥናቶች (Cultural Studies)<br>የጥናት ንድፈ ሐሳብ የተቃኘና ትኩረቱም የነገረ ግብረ ገብ (Morality) ሐተታና ፍካሬ ነው። ጥናቱ<br>በዋነኝነት ደራሲው በ‹‹የህሊና ደወል›› ውስጥ ያነሳቸውን የግብረ ገብ ፈተናዎችና የተጠቀመባቸውን<br>የማርገቢያ ፈሮች ከመሰዋእትነት ምግባራዊ ፍልስፍና (Altruistic morality) ጽንሰ ሐሳብ አንጻር<br>ይተነትናል። በጥናቱ ለመገንዘብ እንደተቻለው የህሊና ደወል ሦስት አንብሮዎችን (Thesis) እንደ መንገድ<br>(Routes) በማበጀት የጠራ የግብረ ገብ ፍልስፍናን ያራምዳል። የመጀመሪያው አንብሮ መስዋዕትነት፣<br>ሁለተኛው ‹‹የፍቅር መሰላሉ ዕውቀት ነው›› ሦስተኛው ደግሞ አንድን ተግባር በተገቢው ሰዓት መከወን<br>(ሥራ በጊዜ) የሚሉ መሆናቸው ለማዬት ተችሏል። ይህ የግብረ ገብ ፍልስፍናም በጥቂቶች መስዋዕትነት<br>የብዙኃን ደስታ ለመፍጠር የሚመኘው የመስዋዕትነት ምግባራዊ ፍልስፍና (Altruistic morality)<br>ተመሳስሎሽ መሆኑ ታይቷል።</p>ደሳለኝ ሥዩም (ዶ/ር)
Copyright (c) 2026
https://creativecommons.org/licenses/by/4.0
2026-08-142026-08-14351121Deictic Features of Demonstratives in Ethiosemitic Languages
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/13988
<p>This paper examines the deictic features of demonstratives in Ethiosemitic<br>languages from a cross-linguistic typological perspective. In most cases,<br>demonstratives in Ethiosemitic languages deictically blend two systems: distanceoriented<br>and person-oriented. As a result, among the studied languages, Amharic<br>and Harari are the three deictic terms that blend the two systems, namely proximal<br>(near to the speaker), distal (far away from both the speaker and the hearer), and<br>the near addressee that refers to a location of the referent farther away from the<br>speaker, and it also indicates that the referent is close to the hearer. However,<br>"Ezha" is four deictic terms, namely proximal (near to the speaker), medial (an<br>entity a bit far from the speaker but still in the vicinity of the speaker), distal (far<br>away from both the speaker and the hearer), and near addressee (it refers to a<br>location farther away from the speaker, and it also indicates that the referent is<br>close to the hearer). Only Tigrinya has the two deictic terms (speaker-proximal and<br>speaker-distal). Demonstratives in the Ethiosemitic languages can be combined<br>with prepositions to refer to the topography, direction, and position of the referent.</p>Elizabeth MinaseDesalegn Hagos
Copyright (c) 2026
https://creativecommons.org/licenses/by/4.0
2026-08-142026-08-143512256Shinasha Number Words Description and Analysis of Modifications1
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/13989
<p>This study deals with the description of Shinasha number words and the analysis of<br>modifications made on borrowed number words in comparison with modifications<br>made on borrowed general words of the language. Background and linguistic data<br>for the study are obtained from primary sources (mainly by the techniques of<br>elicitation with natives, interviewing, and observation) and secondary ones. The<br>conceptual framework employed in the study is simply a general descriptive<br>analysis framework or Basic Linguistic Theory (BLT). The study finds that most<br>of the basic number words of Shinasha are borrowed; and borrowed number words<br>as well as borrowed general words are modified word-externally and wordinternally<br>to conform with the phonological system of the language; that is, foreign<br>sounds and structures are changed to native ones and word forms are modified to<br>appear like the native isolated and constructional phonological forms; even though,<br>borrowed number words exhibit some word-external and word-internal<br>modifications different from borrowed general words. Among all the modifications<br>discussed in the study, the addition of a high tone on some of the vowels of the<br>borrowed number and general words is apparently random, and it is difficult to say<br>where it applies; and some of the other changes (for example, s → sh, k → k’, p →<br>p’) on some words appear to be exceptions to the rule. So, these kinds of<br>apparently random and exceptional changes need further explanatory investigation.<br>Significance-wise, this work aligns with the national agenda of documenting,<br>preserving, and developing Ethiopian languages.</p>Gebre Bizuneh Guadie
Copyright (c) 2026
https://creativecommons.org/licenses/by/4.0
2026-08-142026-08-143515789Copula Constructions in Tsara
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/13990
<p>This paper is mainly concerned with the description and analysis of copula<br>construction in Tsara, a little studied language of the Omotic family, spoken in<br>Southwest Ethiopia Regional State. The study employed Qualitative data analysis<br>methodology, data collection included elicitation, in-depth interview, and group<br>discussion. Secondary data was also used, while data analysis employed Basic<br>Linguistic theory (BLT). In Tsara, copula functions with predicate adjectives and<br>predicate nominals, without taking an object as compared to other verbal clauses.<br>The study has two parts: defines the copula and showing the structure of copula in<br>Tarsa. The first part defines copula as related to equative, attributive, locative,<br>possessive and existential clauses. The second part focuses on the structure of<br>copula. This includes non-tense/present tense, past, future, negative and<br>interrogative copula clauses, which are represented by -be or zero copula, -deenbe,<br>-ʃeri/ʃer-be, and ka- or kaya respectively. It also presents an overview of the<br>copula marker that express the attributive/equative, existential/possessive and<br>interrogative copula constructions. All copula forms discussed so far in the<br>language, are suffixed to either nouns or adjectives. The copula constructions in<br>negative and interrogative clauses are dealt with exhaustively.</p>Mulugeta Seyoum
Copyright (c) 2026
https://creativecommons.org/licenses/by/4.0
2026-08-142026-08-1435190120ብይቶራ በአማርኛ ሥነግጥም በሜሮን ጌትነት ግጥሞች ማሳያነት
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/13991
<p>የዚህ ጥናት ዐቢይ ዓላማ በሜሮን ጌትነት ግጥሞች ምሳሌነት ብይቶራ በአማርኛ ሥነግጥም የሰጠውን<br>አገልግሎት እና ኪናዊ አሠራር በማሳየት ብይቶራው ቅርጻዊ ወይም ጭብጣዊ መሆኑን መለየት ነው።<br>ጥናቱ አስቀድሞ ስለሩሲያ ቅርጻዊነት (Russian Formalism) ንድፈሐሳብ አጀማመር፣ ስለመሠረታዊ<br>መርሆቹ፣ ስለሚከተላቸው ተግባራዊ የአኂያኂያስ መንገዶች፣ ስለጥንካሬዎቹና ድክመቶቹ፣ ሩሲያውያን<br>ቅርጻውያን ስለሥነጽሑፍ ታሪክ ስላላቸው አስተሳሰብ ጉልህ ነጥቦችን በማንሳት በነጥቦቹ ላይ ትኁት<br>ኂሳዊ አስተያየት ይሰነዝራል። ቀጥሎም የዚህኑ ንድፈሐሳብ መሠረታዊ መርሆች ማንጸሪያ (በተለይ<br>“ብይቶራ” በመባል የሚታወቀውን ቴክኒክ መሣሪያ) አድርጎ በአመቺነታቸው የተመረጡትን የሜሮን<br>ጌትነት ግጥሞች አበይቷሪነት እየመረመረ በመተንተን በአማርኛ ሥነግጥም ውስጥ ያለውን የብይቶራ<br>ዓይነት ለይቶ ያሳያል። ከአንድ የዲግሪ ማሟያ ጽሑፍ (ዲማጽ) በስተቀር በዚህ የምርምር ርእሰጉዳይ ላይ<br>ከዚህ ቀደም የተሠራ ምንም ዓይነት አካዴሚያዊ ጥናት ባለመገኘቱም ጉዳዩን በበቂ ሁኔታ ለማስተዋወቅ<br>በመሻት ለንድፈሐሳባዊ ማብራሪያው ሰፋ ያለ ቦታ ይሰጣል። ጥናቱ የሜሮን ጌትነት አብዛኛዎቹ ግጥሞች<br>ተላምዷዊ አስተሳሰባችንን እንግዳ አድርገው በማቅረብ ተፈጥሯዊ መስሎ የሚታየን ብዙው ማኅበረባህላዊ<br>ጉዳይ ሰው-ሠራሽ መሆኑን ልብ እያስባሉ የግንዛቤ ተሐድሶ ለመፍጠር የተከየኑ የምናብ ብጅቶች መሆን<br>አለመሆናቸውን የሚያሳይና የብይቶራውን ዓይነት ለይቶ የሚያመለክት መደምደሚያ ያቀርባል።<br>በመካያውም የገጣሚዋ የብይቶራ ቴክኒክ በሌሎች የሀገራችን ገጣምያን ቢቀሰም ለሥነግጥማችን የሚበጅ<br>መሆኑን የሚጠቁም የይሁንታ አስተያየት በመሰንዘር ይጠናቀቃል።</p>በወንድወሰን አዳነ
Copyright (c) 2026
https://creativecommons.org/licenses/by/4.0
2026-08-142026-08-14351121161የአሌ ቋንቋ ሥርዓተ ድምጽና ሥርዓተ ጽሕፈት
https://ejol.aau.edu.et/index.php/JAELC/article/view/13992
<p>ይህ ጥናት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚነገረውና የኩሺቲክ ቋንቋ ቤተሰብ አባል የሆነው የአሌ ቋንቋን<br>የድምፅ ሥርዓት መመርመር እና ለቋንቋው ተስማሚ የሆነ ሥርዓተ ጽሕፈት መቅረጽ ላይ ትኩረቱን<br>አድርጓል። ጥናቱ በቋንቋው ውስጥ ያሉትን ተነባቢ ድምፆችንና አናባቢ ድምፆችን ጨምሮ የቋንቋዉን<br>ባሕሪ እና የድምፅ ቆጠራ አጠቃላይ መግለጫ ለመስጠት ያለመ ነው። በተጨማሪም እነዚህን ድምፆች<br>ለመወከል የሚያገለግሉትን የአጻጻፍ ሥርዓት ስምምነቶችን ጥናቱ አቅርቧል። በድምጽ ሥርዓቱ እና<br>ሥርዓተ ጽሕፈት መካከል ያለውን ግንኙነት መርምሯል። መረጃ የተሰበሰበው የስዋዴሽ የቃላት ዝርዝር<br>በመጠቀም በቃለ መጠይቅ፣ በጽሑፍ መጠይቅ እና በአፍ መፍቻ ቋንቋ ተናጋሪዎች ምልከታ ነው።<br>ትንታኔው የሚያተኩረው የአሌ ስነ-ድምጽና ስርዓተ-ድምጽ አሐዶችን በመለየት እንዲሁም ውክልናቸውን<br>የሚቆጣጠሩትን የአጻጻፍ መርሆችን በመመርመር ላይ ትኩረት አድርጓል። የጥናቱ ግኝቶች ስለአሌ ቋንቋ<br>ጠለቅ ያለ ግንዛቤ ከመስጠቱም ባሻገር ለወደፊት ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ምርምር ማድረግ ለሚፈልጉ<br>ምሁራን ሁሉ ጠቃሚ መረጃ ይሰጣቸዋል ተብሎ ይታመናል። እንዲሁም የቋንቋው ተናጋሪ የሆነው የአሌ<br>ሕዝብን ለማስተዋወቅ ተጨማሪ መረጃ እና ግንዛቤ እንዲፈጠር አስተዋጽኦ ያደርጋል። ጥናቱ የአሌ ቋንቋ<br>የድምፅ ሥርዓቱ ዝርዝር መግለጫ በመስጠት 32 ተነባቢ ድምፆች እና አምስት አናባቢ ድምፆች ጥናቱ<br>ለይቷል። የተነባቢ ድምፆች መጥበቅና መላላት የትርጉም ለውጥ እንደሚያመጡና እንደዚሁ የአናባቢዎች<br>መርዘምና ማጠር የትርጉም ለውጥ እንደሚያመጡ በጥናቱ ተመላክቷል። በመጨረሻም፣ የተሻለ<br>አገልግሎት ሊሰጥ የሚችለውን ሥርዓተ ጽሕፈት ለቋንቋው ተዘጋጅቷል።</p>ዮናስ በቀለሀረገወይን ከበደ
Copyright (c) 2026
https://creativecommons.org/licenses/by/4.0
2026-08-142026-08-14351162182